በተቀናጀ የማህበራዊ ዘርፍ የ90 ቀናት የእቅድ ክትትል አግባብ ዙሪያ ከሲቪክ ማህራት አመራሮች ጋር ውይይት ተካሄደ።ከሚያዝያ እስከ ሰኔ 2014 በተቀናጀ የማህበራዊ ዘርፍ የ90 ቀናት እቅድ ዙሪያ ከተለያዩ የሲቪክ ማህበራት አመራሮች ጋር በሚያዝያ ወር አፈጻጸም እና ቀሪ ሁለት ወራት አፈጻጸም ክትትል አግባብ ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።በተካሄደው ውይይት የሲቪክ ማህበራቶች ባደራጁት መዋቅር ገለልተኛና ነጻ በሆነ አግባብ ክትትል እንደሚያደርጉ ገልጸው በማህበራዊ ዘርፍ የተለዩት ተቋማት በሚሰጣቸው መርሃግብር መሰረት ዝግጁና ተባባሪ እንዲሆኑ ጠይቀዋል።