በዛሬው ዕለት ቅዳሜ 29-10-2016 የወረዳ 6 አስተዳደር የ2016 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ ስራዎችን የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ደረጃ ፀጋዬ በተገኙበት የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተካሄዷል።
በዚሁ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የፓርቲ ጽ/ቤት የወጣት አደረጃጀት ሀላፊዎች፣ አጠቃላይ የወረዳን አመራሮች፣ የወረዳ 6 ፖሊስ ጣቢያና ጤና ጣቢያ ከስካውት ኢትዮጵያ እንዲሁም የወጣት አደረጃጀቶችን በማቀናጀት 500 ለሚሆኑ አረጋዊያንና አቅመደካሞች በተጨማሪም ለህፃናት የማዕድ ማጋራት አጠቃላይ ንፅህናና እንክብካቤ እንዲሁም አልባሳት የማልበስ ስራ ተከናውኗል።
በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!!