የለውጡ ሂደትን በተመለከተ
“ሀገራዊ ለውጡ እንዲመጣ ያደረጉ ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮች አሉ፤ አንደኛው ነባር ችግሮች ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ወቅታዊ ስብራቶች ናቸው፡፡ ከዚህ አኳያ ነባር ችግሮችን በአገራዊ ምክክር እና ሽግግር ፍትህ ለመፍታት እየተሰራ ነው፡፡ በምክክሩ ነገን የተሻለ ለማድረግ የምንሰራበት ሲሆን፤ ያለፉ በደሎችን ደግሞ በሽግግር ፍትህ የሚፈቱ ይሆናል፡፡ ወቅታዊ ችግሮችን ደግሞ በተቋማት ሪፎርም እየተፈቱ ይገኛሉ፡፡ከዚህ አኳያ ለተመዘገቡ ስኬቶች እውቅና እየሰጠን የሚቀሩትን ደግሞ በጋራ መስራት አለብን፡፡”