#DIREPROSPERITY ሀምሌ 24/2014
የአደረጃጀት ዘርፍ የዓመታዊ ሪፖርት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል።
ከነገ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ከሀምሌ 25 – 27/2014 ከሁሉም ክልሎችና አስተዳደር የአደረጃጀት ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች የሚሳተፉበት አመታዊ ሪፖርት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በአስተዳደሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገር አቀፍ ጉባኤ ይካሄዳል።
በመርሀ-ግብሩ መሰረት የፓርቲ እና መንግስታዊ ስራዎች ከየት ወዴት፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ዓመታዊ ሪፖርት በቅርንጫፍ ዘርፍ ሀላፊዎች እንዲሁም የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሪፖርትና የ2015 በጀት ዓመት መነሻ እቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።