እኛ ብልጽግናዎች ቃላችንን ነን!
ሁሌም ቃላችንን እናከብራለን፤ ለዚህ ቅንጣት ጥርጥር የለንም። በፈተናዎች ብንከበብም፣ በችግር ሸለቆ ውስጥ ብናልፍም፣ ሜዳው ዳገት እንዲሆንብን የሚተጋ ኃይል ቢኖርም ቃላችንን እናከብራለን። እኛ ብልጽግናዎች ቃላችንን ነንና። ቃል እውቀትንና እውነትን መሰረት ሲያደርግ ጥንካሬ ይሰጣል። ተግባራዊ ለማድረግም አቅም ይሆናል። እኛ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት በወንድማማችነት ያስተሳሰሩ የማንነት መገለጫዎች፣ ዓለምን ያስደመሙ ድንቅ እሴቶች፣ ባህልና ወጎች እንዳሉን እናምናለን፤ የእምነታችን ምንጩ እውቀት ነው።